ስራና ደመወዝን

This page was last updated on: 2023-05-06

አነስተኛ የክፍያ ወለል

ብሔራዊ የሆነ አነስተኛ የክፍያ ወለል የለም፡፡ አነስተኛ ክፍያ ያለው በመንግስት ዘርፍ ብቻ ሲሆን ይህም 420 ብር /22 የአሜሪካን ዶላር/ አካባቢ ነው ፡፡ አንዳንድ መንግስታዊ ተቋማት የራሳቸውን አነስተኛ የክፍያ መጠን ያስቀምጣሉ፡፡

በአዲሱ የአሠሪና ሠራተኛ አዋጅ ዝቅተኛ ደመወዝ በሚኒስትሮች ምክር ቤት የደመወዝ ቦርድን ተግባርና ኃላፊነት የሚወሰን ደንብ ሲውጣ ይወሰናል፡፡ የደመወዝ ቦርድ የመንግሥት፤ የአሠሪና ሠራተኛ ተወካዮች እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት ያካትታል፡፡ የደመወዝ ቦርድ የሃገሪቱ የኢኮኖሚ እድገት፤ የሥራ ገበያ ሁኔታ እና የመሳሰሉትን እያስጠና ዝቅተኛ ደመወዝ በየጊዜው ይከልሳል፡፡

የመንግሥት ሠራተኞች መነሻ የደመወዝ ወለል የተወሰነው በብሔራዊ ደረጃ ሆኖ በሠራተኛ አገልግሎት ዓይነትና በሙያ ደረጃ ነው፡፡ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ውሳኔ ላይ ተመሥርቶ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሲቭል ሠርቪስ ሚኒስቴር እንደገለፀው የመነሻ ደመወዝ ወለል ከሌሎች የደመወዝ ደረጃዎች ጋር እንደ ሠራተኛው የሙያና የአገልግሎት ዓይነት የሚከፈል ነው፡፡ የመነሻ ደመወዝ ወለል የሚሰላውም በሰዓት፣ በቀንና በወር የደመወዝ መጠን ነው፡፡

የአሁኑ አነስተኛ የክፍያ ወለል በአነስተኛ ክፍያ ክፍል ውስጥ ይገኛል፡፡

ምንጭ፡ የአሰሪ እና ሰራተኛ አዋጅ ቁጥር 1156/2019 አንቀጽ 55(2) 

መደበኛ ክፍያ

በአሰሪና ሰራተኛ አዋጅ መሰረት ክፍያ ማለት ሰራተኛው/ዋ በስራ ቅጥር ውሉ መሰረት ለሚሰራው/ትሰራው ማግኘት ያለበት/ባት መደበኛ ክፍያ ነው፡፡ ክፍያዎች ከትርፍ ሰዓት ማካካሻ፣ አበሎች፣ ቦነስ፣ ኮሚሽኖች፣ ከደንበኞች ከሚሰጥ የአገልግሎት ክፍያ እና ለተጨማሪ ስራ ከሚከፈሉ ሌሎች ጥቅማ ጥቅሞች ውጪ ናቸው፡፡ ክፍያዎች በአሰሪው አማካኝነት ተቋርጦ ስራ መስራት የማይቻል (ማለትም ቁሳቁሶች እና ጥሬ እቃዎችን ማቅረብ በማቆሙ) ካልሆነ በስተቀር ክፍያዎች ሰራተኛው/ዋ ለሰራው/ችው ስራ ብቻ የሚከፈሉ ናቸው፡፡ በሌላ መልኩ ስምምነት ካልተደረገ በስተቀር የአሰሪ እና ሰራተኛ አዋጅ አሰሪ ክፍያዎችን በጥሬ ገንዘብ በስራ ቀን በስራ ቦታ እንዲከፍል ያስገድዳል፡፡ የክፍያ ቀን በአጋጣሚ (ቀደም ብሎ የተወሰነ ከሆነ) በሳምንት እረፍት ቀን ወይም በህዝብ በአል ቀን ላይ ከዋለ ክፍያዎች በቀጣይ የስራ ቀን የሚከፈል ይሆናል፡፡ ክፍያዎች በሰራተኛው ወይም ሰራተኛው ለወከለው ሰው በቀጥታ ይከፈላሉ፡፡ ክፍያዎች በአይነት ሊከፈሉ ይችላሉ ነገር ግን በጥሬ ገንዘብ በሚከፈሉ ክፍያዎች 30% በላይ መሆን የለባቸውም፡፡

አሰሪው ለሠራተኛው ደመወዙንና ሌሎች ክፍያዎችን በዚህ አዋጅ ወይም በህብረት ስምምነት መሠረት የመክፈል ግዴታ አለበት፡፡ የደመወዝ ክፍያ የሚፈፀምበት ጊዜ በህግ፣ በህብረት ስምምነት፣ በስራ ደንብ ወይም በስራ ውል በተወሰነው መሰረት ይሆናል፡፡

በአጠቃላይ አሰሪው በህጉ ወይም በህብረት ስምምነት ወይም በስራ ደንቦች ካልተደነገገ ወይም በፍርድ ቤት ትእዛዝ ወይም በሰራተኛው የጽሑፍ ፍቃድ ካልሆነ በስተቀር ክፍያዎችን ለመቀነስ አይፈቀድለትም፡፡ የሚቀነሰውም መጠን ሰራተኛው በየወሩ ከሚከፈለው ክፍያ 1/3ኛ መብለጥ የለበትም፡፡ አሰሪው የሰራተኛው ፊርማ ያለበት ልዩ ስምምነት ከሌለ በስተቀር በመዝገቡ ውስጥ ያልተጣራ ክፍያ፣ የክፍያዎችን ስሌት ዘዴ፣ ሌሎች ተለዋዋጭ ጥቅማ ጥቅሞች፣ የተቀናሽ መጠን እና አይነት እና የተጣራ ክፍያ እና ሌሎች አግባብነት ያላቸው መግለጫዎችን  የሚያሳይ የክፍያ መዝገብ የመያዝ ግዴታ አለበት፡፡  እንዲህ አይነቱ መዝገብ ለሁሉም ሰራተኞች ተደራሽ መሆን እና ሰራተኛው ጥያቄ ሲያቀርብ አመዘጋገቦቹ ይብራሩለታል፡፡

የኢትዮጵያ መንግስት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሐምሌ 2011 ዓ.ም የፀደቀውን አዲሱን የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 (1156/2019) ነሄሴ 30 2011 ዓ.ም አሳትሟ፡፡ አዲሱ የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1156/2019ን እንዲሁም በ1997, 1998 and 2002 የተደረጉትን ማሻሻያዎች ይሽራል፡፡

ምንጭ፡ የአሰሪ እና ሰራተኛ አዋጅ ቁጥር 1156/2019 አንቀጽ 53-60 

ስራና ደመወዝን የተመለከቱ ደንቦች

  • የአሰሪና ሰራተኛ ዓዋጅ ቁ. 377/2003 / Labour Proclamation No.377/2003
loading...
Loading...