This page was last updated on:
2025-06-22
የትርፍ ሰዓት ስራ ክፍያ
መደበኛ የስራ ሰዓት በቀን 8 ሰዓት እንዲሁም በሳምንት 48 ሰዓት ነው፡፡ የአሰሪና ሰራተኛ አዋጅ ‹‹መደበኛ የስራ ሰዓት›› ማለት ሰራተኛው በትክክል ስራውን የሚሰራበት ወይም እራሱን ለስራ ዝግጁ አድርጎ በህጉ፣ በህብረት ስምምነት ወይም በስራ ደንቦች መሰረት በስራ ቦታ የሚገኝበት ሰዓት ማለት እንደሆነ ይገልጻል፡፡ በሚኒስቴሩ መመሪያ መሰረት ለኢኮኖሚ ዘርፎች፣ ለኢንዱስትሪዎች ወይም ልዩ የስራ ሁኔታዎች ባሉባቸው ስራዎች የሰራተኛው ደመወዝ ሳይቀነስ በሰራተኛው የስራ ሰዓት ሊቀነስ ይችላል፡፡ የስራ ሰዓቶች ለሳምንቱ የስራ ቀናት እኩል ይደለደላሉ፡፡ ነገር ግን የስራው ባህሪይ ቢያስገድድ በማናቸውም የሣምንቱ የስራ ቀኖች ሰአቶችን ማሣጠርና ልዩነቱን ለተቀሩት ቀኖች ማደላደል ይቻላል፡፡ የስራ ሰዓታት በቀን እስከ 10 ሰዓታት ማራዘም ይቻላል::
በሕብረት ስምምነት ወይም በሥራ ሕጎች ካልተገለፀ በስተቀር መደበኛ: የሥራ ሰዓት ገደብ ለንግድ ተጓዦች ወይም ተወካዮች ተፈጻሚ አይሆንም።
ከመደበኛ የሥራ ሰዓት በላይ የሚሠራ ሥራ የትርፍ ሰዓት ሥራ ነው፡፡ በአደጋ ጊዜ (አደጋ ሲደርስ ወይም የሚደርስ መሆኑ ሲያሰጋ) ከአቅም በላይ የሆነ ሁኔታ ሲያጋጥም፤ በአስቸኳይ መሰራት ያለበት ሥራ ሲያጋጥም እና በማያቋርጥና ተከታታይ ሥራ ላይ ከሥራ የቀሩ ሠራተኞችን ለመተካት ካልሆነ በስተቀር አንድ ሠራተኛ የትርፍ ሰዓት ሥራ እንዲሠራ አይገደድም፡፡ የትርፍ ሰዓት ሥራ በቀን ከ4 ሰዓት ወይም በሣምንት ከ12 ሰዓት ላይበልጥ ይችላል፡፡ አንድ ሰራተኛ በስራ ቀናት እንዲሰራ ከተወሰነው መደበኛ የስራ ሰዓት ማለትም በቀን 8 ሰዓት እና በሣምንት 48 ሰዓት ውጭ ቢሰራ ከመደበኛ ደመወዙ በተጨማሪ ቀጥሎ በተመለከተው ይከፈለዋል፡፡
- ከንጋቱ 12 ሰዓት እስከ ምሽቱ 4 ሰዓት ለሚሠራ የትርፍ ሰዓት ሥራ ለመደበኛ ሥራ በሰዓት የሚከፈለው ደመወዝ በ150 % ተባዝቶ ይከፈላል
- ከምሽቱ 4 ሰዓት እስከ ንጋቱ 12 ሰዓት ለሚሠራ የትርፍ ሰዓት ሥራ ለመደበኛ ሥራው በሰዓት የሚከፈለው ደመወዝ በ175 % ተባዝቶ ይከፈላል
- በሳምንት የዕረፍት ቀን የሚሠራ የትርፍ ሰዓት ሥራ ለመደበኛው ሥራው በሰዓት የሚከፈለው ደመወዝ በ200% ተባዝቶ
ምንጭ፡ የአሰሪ እና ሰራተኛ አዋጅ ቁጥር 1156/2019 አንቀጽ 61-68
የምሽት ስራ ክፍያ
በአሰሪና ሠራተኛ አዋጅ መሠረት የምሽት ስራ ከምሽት 4 ሰዓት እስከ ንጋቱ 12 ሰዓት የሚሠራ ሥራ ማለት ነው፡፡ በአሰሪ እና ሰራተኛ አዋጁ ላይ አሰሪዎቹ ለምሽት ሠራተኞች ክፍያ እንዲፈፅሙ የሚያደርግ አንቀፅ የለም፡፡ ከፍተኛ ክፍያዎች የሚፈፀሙት የቀን ሠራተኞች ሆነው በምሽት ትርፍ ስራ ለሚሠሩ ነው፡፡ ማካካሻ ክፍያዎችን ለመክፈል የሚያስገድድ የተለየ ድንጋጌ በአሰሪና ሰራተኛ አዋጁ ውስጥ የለም፡፡ የምሽት ሰዓታት ትርፍ ሰዓታት ከሆኑ: ለሠራተኛው የመደበኛውን ክፍያ 150% ማግኘት አለበት፡፡
ምንጭ፡ የአሰሪ እና ሰራተኛ አዋጅ ቁጥር 1156/2019 አንቀጽ 68
በምትክ የሚሰጥ ዕረፍት
ከባድ የስራ መስተጓጎልን ለማስወገድ ሲባል፡ ሰራተኞች በአደጋ ምክንያት (አደጋ ሲኖር ወይም አደጋ ይደርሳል ተብሎ ሲገመት)፣ ወይም ከአቅም በላይ የሆነ ሁኔታ ሲያጋጥም ወይም አስቸኳይ ስራ ሲኖር: በሳምንት የእረፍት ቀን ወይም በህዝባዊ በዓል ቀን ስራ እንዲሰሩ ሊደረጉ ይችላሉ፡፡
አንድ ሰራተኛ ማካካሻ የሚያገኝበት የበዓል ቀን ከመድረሱ በፊት የስራ ውሉ/ሏ ቢቋረጥ ማካካሻ የሚያገኝ/የምታገኝ ይሆናል፡፡ በህዝባዊ በዓላት ቀናት ለሚሰሩ ሰራተኞች የሚሰጥ የምትክ ዕረፍት ጊዜን የተመለከተ ድንጋጌ ግን የለም፡፡
ምንጭ፡ የአሰሪ እና ሰራተኛ አዋጅ ቁጥር 1156/2019 አንቀጽ 71
የሳምንት መጨረሻ / የህዝባዊ በዓላት ስራ ክፍያ
ሰራተኞች በሳምንት የእረፍት ቀናት ወይም ህዝባዊ በዓል ቀናት እንዲሰሩ ሊደረጉ ይችላሉ፡፡ እንዲህ አይነቱ ሁኔታ ሲኖር፡ ማለትም ሰራተኞቹ በህጋዊ/ህዝባዊ በዓላት ቀናት እንዲሰሩ ከተደረገ፡ የማካካሻ ክፍያ መደበኛ የሰዓት ክፍያቸው ከሚከፈላቸው በ200% ተባዝቶ ይከፈላቸዋል፡፡
ምንጭ፡ የአሰሪ እና ሰራተኛ አዋጅ ቁጥር 1156/2019 አንቀጽ 75
መካካሻ የተመለከቱ ደንቦች
-
የአሰሪና ሰራተኛ አዋጅ ቁ. 1156/2011 / Labour Proclamation No. 1156/2019