የግዳጅ ስራ

This page was last updated on: 2023-05-06

የግዳጅ ስራ

የግዳጅ ስራ በህገ መንግስቱ የተከለከለ ነው፡፡ - አንድ ሰው ሌላውን በማስፈራራት፣ በጉልበት፣ በማጭበርበር ወይም ሌላ ሕገ-ወጥ መንገድ በመጠቀም አንድን ሥራ ወይም የተለዩ የቅጥር ሁኔታዎችን እንዲቀበል ቢያደርግ፣ ወይም አሠሪው የቅጥር ሁኔታን እንዲቀበል ወይም እንዲቀይር ለማስገደድ አለመስራት ወይም መለገም (refuse labor or withhold labor) ቅሬታ በሚቀርብበት ወቅት ቢያንስ በሶስት ወራት ቀላል እስር ወይም ለገንዘብ ቅጣት ይዳርጋል፡፡

ፀረ ህገ-ወጥ የሰው ማዘዋወር ህግ ሰውን በህገ-ወጥ መንገድ ለቤት ውስጥ ሥራ ቅጥር ወይም በውጭ ሀገር ለማስቀጠር በሚል ስበብ ማዘዋወርን ይከላከላል፡፡ ለብዝበዛ የሰጠው ትርጉም የጉልበት ብዝበዛን፣ የግዳጅ ሥራን ወይም ያለውዴታ አገልጋይነትን ያካትታል፡፡ ይህ የወንጀል ድርጊት ከ15 እስከ 25 ዓመት ጽኑ እሥራትና ከብር 150,000 እስከ 300,000 ቅጣት ያስቀጣል፡፡ 

ምንጭ፡  በ1994 የወጣው የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፑብሊክ ህገ-መንግስት አንቀጽ 42(2 እና 3) እና የወንጀለኛ መቅጫ አዋጅ ቁጥር 414(2004); 2፣3 ህገወጥ የሰው ማዘዋወር መከላከልና ማቆም በማጭበርበር/በማዘዋወር አዋጅ ቁጥር 909/2015

ስራን የመቀየር ነፃነት እና ስራን የመተው መብት

ሰራተኞች ለአሰሪያቸው ማስታወቂያ ከሰጡ በኋላ ስራቸውን የመቀየር መብት አላቸው:: ይህንን በተመለከተ ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት እባክዎን የቅጥር ደህንነት የሚለውን ክፍል ይመልከቱ፡፡

ምንጭ፡ የአሰሪና ሰራተኛ አዋጅ ቁጥር 1156/2019 አንቀጽ 26-35

ኢ-ሰብአዊ የስራ ሁኔታ

የስራ ሰዓት ከመደበኛ የሥራ ሰዓት በቀን ከ8 ሰዓት ወይም በሣምንት ከ48 ሰዓት በላይ ሊሄድ ይችላል፡፡ ሆኖም የትርፍ ሰዓት ሥራ በቀን ከ4 ሰዓት ወይም በሳምንት ከ12 ሰዓት ሊበልጥ አይችልም፡፡ ከፍተኛው የስራ ሰዓት ትርፍ ሰዓትን ጨምሮ (48 ሰዓት + 12 ሰዓት) በሣምንት 60 ሰዓት ነው፡፡ ማንኛውም ሠራተኛ የትርፍ ሰዓት ሥራ እንዲሠራ አይገደድም አደጋ ሲደርስ ወይም የሚደርስ መሆኑ ሲያሰጋ፤ ከአቅም በላይ የሆነ ሁኔታ ሲያጋጥም፣ በአስቸኳይ መሰራት ያለበት ሥራ ሲያጋጥም ወይም በማያቋርጥና ተከታታይ ሥራ ላይ ከሥራ የቀሩ ሠራተኞችን ለመተካት ካልሆነ በቀር፡፡ ፡

ምንጭ፡-የተሻሻለው የአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 አንቀፅ 61-67

loading...
Loading...