የህመም ፈቃድ ከክፍያ ጋር
የአሰሪና ሰራተኛ አዋጁ ህመም መኖሩ ብቃት ባለው ዶክተር ከተረጋገጠ የሙከራ ጊዜውን ላጠናቀቀ ሰራተኛ እስከ 6ወር ድረስ የህመም ፍቃድ ከክፍያ ጋር እንደሚሰጥ ይደነግጋል፡፡ አንድ ሰራተኛ በስራ ላይ ከሚደርስ ጉዳት ሌላ በሆነ ህመም መስራት የማይችል/የማትችል ከሆነ የህመም ፍቃድ የማግኘት መብት አለው/አላት፡፡ አንድ ሰራተኛ በህመም ምክንያት ከስራ መቅረቱን ለአሰሪ መግለጽ እና በመንግስት እውቅና ካገኘ የህክምና ድርጅት የህክምና ማስረጃ ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
አሰሪው የህመም ፍቃድ እንደሚከተለው ሊሰጥ ይችላል፡-
. በህመም ፍቃድ የመጀመሪያው ወር 100% ክፍያ
. በሁለተኛ እና በሶስተኛ ወር የህመም ፍቃድ 50%
. ከአራተኛ እስከ ስድስተኛ ወር ድረስ የህመም ፍቃድ ያለክፍያ
ምንጭ፡ የአሰሪና ሰራተኛ አዋጅ ቁጥር 1156/2019 አንቀጽ 85-86; ISSA የሀገር ፕሮፋይል
የህክምና እንክብካቤ
በ2010 ዓ.ም የፀደቀው የማህበራዊ ጤና መድህን አዋጅ ለሰራተኞች ስለሚቀርቡ የህክምና እና የጤና አገልግሎቶች ይደነግጋል፡፡ ሁሉም ሰራተኞች የማህበራዊ ጤና መድህን መርሀ ግብር አባል መሆን ይጠበቅባቸዋል፡፡ አንድ ሰራተኛ በሥራ ላይ ጉዳት ሲደርስበት የጠቅላላና የልዩ ሕክምና እንዲሁም የቀዶ ሕክምና ወጪዎችን፤ የሆስፒታልና የመድሃኒት ወጪዎችን እና የማንኛውም አስፈላጊ ሰው ሰራሽ ምትክ ወይም ተጨማሪ አካሎችና የአጥንት ጥገና ወጪዎችን አሠሪው ይከፍላል፡፡ ነገር ግን የዚህ አዋጅ አፈጻጸም እንዲዘገይ ተደርጓል።
የማህበረሰብ የጤና መድህን አዋጅ ቁጥር 1273/2014 ሰራተኞችን ብቻ ሳይሆን አጠቃላይ ማህበረሰቡን ተጠቃሚ በሚያደርግ መልኩ የተረቀቀ ነው።
ምንጭ፡- ISSA የሀገር ፕሮፋይል ፤ የአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1156/2019 ፣ አንቀፅ 105
የስራ ደህንነት
የታመመ አንድ ሰራተኛ የስራ ውሉ በህመም ፍቃዱ ወቅት የተጠበቀ ይሆናል፡፡ አሰሪው ሰራተኛውን የ6 ወር የህመም ፈቃዱ ሳያልክ በህመሙ ምክናያት ከስራው ሊያባርረው አይችልም። ሰራተኛን የ6ወር የህመም ፈቃድ ሳይጨርስ ከስራው በህመም ምክናያት ማሰናበት ህገወጥ የስራ ማሰናበት ይሆናል።
ምንጭ፡- የአሰሪና ሰራተኛ አዋጅ ቁጥር 1156/2019 አንቀጽ 85-86