This page was last updated on: 2023-05-06 የአባትነት ፈቃድ የ2003ቱ የአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ አዋጅ የትዳር ጓደኛ ስትወልድ ሰለሚሰጥ ፍቃድ የሚደነግግ አንቀፅ አልነበረውም፡፡ በ2011ዓ.ም በተሻሻለው የአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ አዋጅ አንድ ወንድ ሠራተኛ የትዳር ጓደኛው ስትወልድ ደመወዝ የሚከፈልበት 3 ተከታታይ ቀናት ፈቃድ ከክፍያ ጋር ይሰጠዋል፡፡ ምንጭ፡- የተሻሻለው የአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 አንቀፅ 81 እና ስራ የወላጅነት ፈቃድ የወሊድ ፈቃድ ከወጡ በኋላ ለአዲሶቹ ወላጆች የወላጅ ፈቃድን በሚደግፍ ሕግ ውስጥ የሉም ፡፡ ህፃናት ልጆችና ሌሎች የቤተሰብ ሀላፊነት ላሉባቸውሠራተኞች የሚበጁ አማራጭ በህጉ ውስጥ የወላጆች እና የቤተሰብ ሀላፊነት ያለባቸው ሰራተኞች የስራና ህይወት ሚዛን ይጠብቁ ዘንድ አጋዥ የሆኑ ድንጋጌዎች የሉም፡፡ ተያያዥ ርዕሶች ወሊድ እና ሥራ ስራና ህመም የዓመት ዕረፍት እና በሳምንታዊና በህዝብ በዓላት መስራት